፫ኛው ሀገር አቀፍ የስብከተ ወንጌል ቀን መክፈቻና ማብሰሪያ መርሐ ግብር በተመረጡ 12 አብያተ ክርስቲያናት ተከናወነ!!
ሚያዝያ ፲፰ ቀን ፪፻፲፰ ዓ.ም.)
ስ/ወ/ሐ /ተልእኮ ሚዲያ /አ/አ/
የስብከተ ወንጌልና ሐዋርያዊ ተልእኮ መምሪያ በወንጌል ሕይወታችን ሆነ” በሚል መሪ ቃል ለ፫ኛ ጊዜ ሀገር አቀፍ በሆነ መልኩ በቅድስት ሥላሴ ዩንቨርስቲ ሁለገብ አዳራሽ ሚያዝያ 19 ቀን 2018 ዓ.ም የሚያከብረውን “የስብከተ ወንጌል ቀን” የማብሰሪያ መርሐ ግብር በዛሬው ዕለት በተመረጡ አድባራትና ገዳማት በተመሳሳይ ሰዓት በስብከተ ወንጌል ጉባኤያት ተከብሮ ውሏል።
በዚህ ፫ኛው የስብከተ ወንጌል ቀን ማብሰሪያ በአዲስ አበባና ሸገር ከተማ አህጉረ ስብከት ከተማ ሥር በሚገኙ የተመረጡና ከፍተኛ የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴ በሚደረግባቸው 12 ገዳማትና አድባራት የተደረገ ሲሆን በዕለቱም በመምሪያው ጋባዥነትና የወንጌል መምህራንና ዘማርያን ተጋብዘው ሰፊ አገልግሎት ተሰጥቷል።
በየቦታው በተመደቡ አስተባባሪዎች አማካኝነት የስብከተ ወንጌል ቀንን ዓመታዊ ጉባኤ በማድረግ መዘከር ያስፈለገበት በጨለማ ውስጥ ያለነውን ወደ ብርሃን ለማውጣት፣ ከኃጢአት ወደ ጽድቅ ለመመለስና ሌሊት የሆነውን ሕይወታችንን ወደ ቀን በንስሐ ለመመለስ
መሆኑ ተወስቷል።
በተጨማሪም መምሪያው ከሁሉም አህጉረ ስብከትና የትምህርት ተቋማት ጋር በመናበብና በመተባበር የስብከተ ወንጌል እንቅስቃሴን ለማጠናከር እያከናወነ ያለውን ተግባር ተስፋ የሚጣልበት መሆኑ በብዙዎች ምስክርነት አግኝቷል።
መርሐ ግብሩ ነገ ሰኞ ሚያዝያ ሚያዝያ ፲፱ ቀን ፪፻፲፰ ዓ.ም ቀጥሎ የሚውል ሲሆን፣ “ሀገር አቀፍ ዓመታዊ የወንጌል ቀን እና የምክክር ጉባኤ” በቅድስት ሥላሴ ዩኒቨርሲቲ ሁለገብ መሰብሰቢያ አዳራሽ ከረፋዱ 2:30 ጀምሮ እንደሚካሄድ ታውቋል።
