መድኃኔዓለም
ኦርቶዶክሳዊት ተዋሕዶ ቤተክርስቲያናችን ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን መድኃኔዓለም”ብላ ስትጠራው ” የዓለም ኹሉ መድኃኒት አንተ ነኽ” እያለች ነው።
ይኽም ጌታችን አምላካችንና መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ መላውን ዓለም ከዘላለም ሞት፣ ከሲኦል ባርነትና ከሰይጣን አገዛዝ ነፃ ያወጣበትን ታላቅ የማዳን ሥራ የሚገልጽ ስም በመኾኑ ነው።
ለዚህም ስያሜ መነሻ የሆናት ቅዱሱ መጽሐፍ ሲሆን ይኸውም ክብር ይግባውና እርሱ ገና በጽንሰቱ፤ መልአኩ ቅዱስ ገብርኤል ለቅዱስ ዮሴፍ “ሕዝቡን ከኃጢአታቸው ያድናቸዋልና ስሙን ኢየሱስ ትለዋለህ” (ማቴ ፩፡፳፩) በማለት የመድኃኒትነት ስሙን ከነ ግብሩ አብስሯል።
በዚኽ ያላበቃው ቸርነቱ በልደቱም ቀጥሎ እርሱ በተወለደ ጊዜ መላእክት ለእረኞች “ለሕዝቡ ኹሉ የሚኾን ታላቅ ደስታ… መድኃኒት እርሱም ክርስቶስ ጌታ የሆነ ተወልዶላችኋል” (ሉቃ ፪፡፲) በማለት የዓለም መድኃኒትነቱን መስክረዋል።
ኋላም በመዋዕለ ሥጋዌ ትምህርቱ፤ ሳምራዊቷ ሴት ያደረገላትን ነገር ኹሉ ለሴቶቹ ከመሰከረችላቸው በኋላ “አኹን የምናምን ስለ ቃልሽ አይደለም፥ እኛ ራሳችን ሰምተነዋልና፤ እርሱም በእውነት ክርስቶስ የዓለም መድኃኒት እንደ ኾነ እናውቃለን ይሉአት ነበር።”
(ዮሐ. ፬፥፵፪)
መድኃኔዓለም አባታችን በቤታችን የጎደለውን በምሕረቱ ይሙላልን።
የጎበጠውን ኑሯችንን ያቅናልን።
በእልፍኛችን ተሸሸግን ያነባነውን እንባችንን ያብስልን።
አሜን
